ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መድረክ የበጎ ፈቃደኞች ምእመናን ስብስብ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት እና ቀኖና አክብረው ለቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት መሻሻል እና የምእመናን ደኅንነት ጉዳይ ላይ ለማገዝ የበኩላቸውን ከሚወጡ አካላት ሁሉ ጋር ተባብሮ ይሠራል። ሆኖም ግን በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ እንጂ የየትኛውም ማኅበር ወይም ተቋም ተቀጥላ አይደለም። ይንን አቋም የሚወስድበት ምክንያትም በገለልተኛነትና በነጻነት ተንቀሳቅሶ ማእከላዊ በሆነ መንገድ ሁሉንም ለማገልገል እንዲያስችለው ነው።